በፍትሕና የሕግ ማስከበር ዘርፍ፣ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥና የዜጎችን ፍትሕ የማግኘት መብት ለማስከበር ተቋማዊ ሪፎርሞች ተተግብረዋል። የፍትሕ አካላትን የአገልግሎት አሰጣጥ ቀልጣፋና ግልጽ ለማድረግ፣ የዓቃቤ ሕግና የፍርድ ቤቶችን አሠራር በዲጂታል ሥርዓት የመደገፍ ሥራ ተጀምሯል። ከዚህ በተጨማሪ በየደረጃው የሚገኙ የፖሊስና የጸጥታ መዋቅሮችን አቅም በመገንባት፣ የሙስና እና የህገ-ወጥ ድርጊቶች የመከላከል ሥራዎች በትኩረት ተከናውነዋል።
በባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ዘርፍ፣ የክልሉን ብዝሃ-ባህልና ተፈጥሯዊ ሀብቶች ለማስተዋወቅና ለልማት ለማዋል ሰፊ ጥረት ተደርጓል። በክልሉ የሚገኙ የታሪክ፣ የባህልና የተፈጥሮ መስህቦችን (የታላቁ ሕዳሴ ግድብን ጨምሮ) ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ጎብኚዎች ለማስተዋወቅ የቱሪዝም ፕሮሞሽን ሥራዎች ተከናውነዋል። የብሔረሰቦችን ባህል፣ ቋንቋና እሴቶች የሚያጎሉ ሁነቶችና የባህል በዓላት ተዘጋጅተው የተካሄዱ ሲሆን፣ በስፖርቱ ዘርፍም የወጣቶችን ተሳትፎ የሚያሳድጉ የውድድር መድረኮች ተመቻችተዋል።
በመንግሥት ኮሙኒኬሽንና የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ፣ የመንግሥትን ፖሊሲዎች፣ ስትራቴጂዎችና የልማት አፈጻጸሞች ለሕዝቡ ክፍትና ግልጽ በሆነ መልኩ የማድረስ ሥራ ተከናውኗል። የሐሰተኛ መረጃዎችንና አ አሳሳች ትረካዎችን በመከላከል፣ ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃዎችን ለሕዝብ ለማቅረብ የዲጂታል ሚዲያ አማራጮችና የመገናኛ ብዙኃን አቅም እንዲጎለብት ተደርጓል። ይህም የመንግሥትና የሕዝብ ግንኙነትን የበለጠ በማጠናከር ለልማትና ለሰላም ግንባታው አዎንታዊ አስተዋፅኦ አበርክቷል።





 ታጣቂዎች የተዘጋጀላቸውን የተሃድሶ ስልጠና አጠናቀው ዛሬ ተመርቀዋል.jpg)
 ታጠቂ ቡድን ጋር የተደረሰው የሰላም ስምምነት.jpg)


 ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግሥት ጋር አብሮ የመስራት የውል ስምምነት.jpg)


