በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግሥት ባለፉት አምስት ዓመታት ከተከናወኑ በርካታ ተግባራት መካከል ዘላቂ ሰላምና ደኅንነትን ማረጋገጥ የሁሉም ልማቶችና አገራዊ ዕድገቶች መሠረት ሆኖ ተወስዷል። ክልሉ የነበረበትን ውስብስብ የደኅንነት ሥጋት በመረደታ እና ዘላቂ መፍትሔ ማምጣት የሚቻለው በሰላማዊ መንገድ ብቻ እንደሆነ በማመን፣ የክልሉ መንግሥት የሰላም በሮችን ሙሉ በሙሉ ክፍት በማድረግ ሰፊ የውይይትና የድርድር ስትራቴጂዎችን ተግብሯል።
በዚሁ መሠረት በክልሉ ይንቀሳቀሱ ከነበሩ ታጣቂ ኃይሎች ጋር የተሳኩ የሰላም ውይይቶች የተካሄዱ ሲሆን፣ በተለይም ከቤኒሻንጉል ሕዝብ ነጻነት ንቅናቄ (ቤህነን) እና ከጉሙዝ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጉህዴን) ጋር ታሪካዊ የሆኑ የሰላም ስምምነቶች ተፈራርመዋል። በእነዚህ የሰላም ስምምነቶች መሠረት የድርጅቶቹ አመራሮችና አባላት ትጥቃቸውን ፈተው በምህረት ወደ ማኅበረሰቡ እንዲቀላቀሉ የተደረገ ሲሆን፣ የፖለቲካ ጥያቄዎቻቸውን በሰላማዊና በዴሞክራሲያዊ መንገድ የሚያንፀባርቁበት፣ በክልሉ የልማትና የመልካም አስተዳደር እንቅስቃሴዎችም በባለቤትነት የሚሳተፉበት አስተማማኝ ሁኔታ ተፈጥሯል። ከዚህም በተጨማሪ ሌሎች የቦታው ታጣቂ ቡድኖችም የሰላሙን ጥሪ ተቀብለው ትጥቅ በመፍታት ወደ ሰላማዊ ሕይወት እንዲመለሱ ተደርጓል።
እነዚህ አበይት የሰላም ስምምነቶችና የተቀናጁ የሕግ ማስከበር ሥራዎች በክልሉ አስተማማኝ መረጋጋት እንዲሰፍን ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርገዋል። በዚህም ሂደት በክልሉ ተለይተው ከነበሩት 156 የጋራ ሥጋት ቀጠናዎች ውስጥ 130 የሚሆኑት (83.3 በመቶ) ሙሉ በሙሉ ወደ ሰላማዊ ቀጠናነት እንዲሸጋገሩ ተደርጓል
- የሰላሙ መመለስ ያስገኛቸው አመርቂ ውጤቶችም እንደሚከተለው ተገልጸዋል፦
- የተቋረጡ ልማቶችና አገልግሎቶች መመለስ፦ በጸጥታ ችግር ምክንያት ተቋርጠው የነበሩ በርካታ ትምህርት ቤቶች፣ ጤና ጣቢያዎችና የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ዳግም ወደ ሥራ እንዲገቡ ተደርጓል።
- የመሰረተ ልማቶች ጥገና፦ በግጭት ምክንያት አገልግሎታቸው ተቋርጦ የነበሩ የኤሌክትሪክና የቴሌኮም መስመሮች (ለምሳሌ፦ በሰዳልና ምዥጋ ወረዳዎች) አስፈላጊው ጥገና ተደርጎላቸው አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል።
- ዜጎችን መልሶ ማቋቋም፦ በግጭቶች ምክንያት ተፈናቅለው የነበሩ ወገኖች ሙሉ በሙሉ ወደ ቀደመ ቀያቸው እንዲመለሱ፣ የመልሶ ማቋቋምና የሰብዓዊ ድጋፍ ሥራዎች በተቀናጀ መልኩ እንዲከናወኑ ተደርጓል።
በአጠቃላይ ባለፉት አምስት ዓመታት በሰላምና ደኅንነት ዘርፍ የተመዘገቡት እነዚህ ስኬቶች ክልሉ ወደ መደበኛ የልማት፣ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ እድገት ምዕራፍ እንዲሸጋገር አስተማማኝ መሠረት ጥለዋል።





 ታጣቂዎች የተዘጋጀላቸውን የተሃድሶ ስልጠና አጠናቀው ዛሬ ተመርቀዋል.jpg)
 ታጠቂ ቡድን ጋር የተደረሰው የሰላም ስምምነት.jpg)


 ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግሥት ጋር አብሮ የመስራት የውል ስምምነት.jpg)


